Naima Saladin

Naima Saladin

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Naima Saladin, Health/Beauty, Dire, Addis Ababa.

23/07/2026
Photos from Harari Region Prosperity Party - ብልፅግና's post 23/07/2026
Photos from Ethiopian News Agency/Afaan Oromoo's post 23/07/2026
23/07/2026

በሀረሪ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ

በሀረሪ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነው ነፃ የህክምና አገልግሎት "በጎነት ለጤናማ ማህበረሰብ" በሚል ሀሳብ ነው እየተሰጠ የሚገኝው።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብዲ አሚን እንደገለጹት እየተሰጠ የሚገኝው ነፃ የምርመራና የህክምና አገልግሎት አቅመ ደካማ ለሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

ነፃ የህክምና አገልግሎቱ በበጎ ፍቃደኛ የጤና ባለሙያዎች አማካኝነት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው አገልግሎቱም በመንግስትና በተመረጡ የግል ጤና ተቋማት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

እየተሰጡ ከሚገኙ የጤና ምርመራዎች መካከልም የስኳር ህመም፣ የደም ግፊት፣ ከአንገት በላይ፣ የቆዳና የአይን እና የልብ ሕመም ምርመራና ሕክምና እንዲሁም ሌሎች ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ይገኙበታል ብለዋል ከዚህ በተጨማሪም ከ5 ሺህ በላይ የደም ልገሳ መርሃ ግብሮች እንደሚካሄድ ገልጸዋል።

በምርመራው ወቅትም ተጨማሪ ህክምና ምርመራ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ወደ ሚመለከታቸው የጤና ተቋማት በመላክ አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

ከዚህ በተጨማሪም በዘመቻው ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስመልክቶ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።

ዘመቻው የጤና አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የህዝብን የጤና ንቃት ለማሳደግና የመረዳዳት ባህልን ለማሳደግ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።

በመሆኑም ኅብረተሰቡ ይህንን በመገንዘብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

22/07/2026

"ማረሚያ ቤቱ ታራሚዎችን በሙያና ስነ ምግባር በማነፅ ብቁ ዜጎች የሚፈጠሩበት እንዲሆን ትኩረት መሰጠቱን የሀረሪ ክልል ማረሚያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አድናን አህመድ ገለፁ።

ኮሚሽነሩ የኮሚሽኑን የቀጣይ ግዜ አቅጣጫ በማስመልከት በሰጡት መግለጫ የታራሚዎችን ሰብዓዊ መብት በመጠበቅ የተመዘገበውን ውጤት በ 2019 ለማጎልበት ይሰራል ብለዋል።

በተለይ ታራሚዎችን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች እንዲሰለጥኑ በማስቻል የተመዘገበውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ነው የገለፁት።

ታራሚዎች በማረሚያ ቆይታቸው የባህሪ ለውጥ እንዲያመጡ በማስቻል ወንጀልን የሚፀየፉ ዜጎች እንዲሆኑ ለማስቻል በትኩረት ይሰራል።

ኮሚሽኑ ታራሚዎች የእርምት ግዜያቸውን አጠናቀው ከማህበረሰቡ ጋር በሚቀላቀሉበት ግዜ በሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ በመሰማራት ሰላማዊና አምራች ሀይል በመሆን ገበያውን እንዲቀላቀሉ ማስቻል አላማው አድርጎ እየሰራ ነው።

በዚህም የማረሚያ ቤቱን የማረም ማነጽ ስርዓት ይበልጥ በማሻሻል ታራሚዎች በስነ ምግባርና ሙያ ታንፀው እንዲወጡ ለማስቻል ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ሲሉ ገልፀዋል።

ታራሚዎችን ገበያ ላይ በሚፈለጉ የሙያ ዘርፎች ይበልጥ ለማብቃት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ኮሚሽኑ ከክልሉ ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር የጀመረው የወረቀት አልባ ሶፍትዌር የማበልጸግ ሥራ በያዝነው የበጀት ዓመት እንዲጠናቀቅ በማድረግ ዘመናዊ፣ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት ያስችላል ብለዋል።

ማረሚያ ኮሚሽኑ የሕግ ታራሚዎችን የማረምና ማነጽ ስርዓቱን ይበልጥ በማሻሻል የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ኮሚሽነር አድናን አህመድ የገለፁት።

Want your business to be the top-listed Beauty Salon in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Dire
Addis Ababa